ከድሬዳዋ አስተዳደር እና ከድሬዳዋ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የተሰጠ መግለጫ.
ትላንት ማታ በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ በንፁሃን ዜጎች ላይ በደረሰው እጅግ አሰቃቂ የወገን ህይወት መጥፋት የድሬዳዋ አስተዳደር፣ የድሬዳዋ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት እና ነዋሪዎች እጅጉን አዝነናል፤ በሰላማዊና ንፁሃን ዜጎች ላይ በደረሰው አረመኔያዊና ዘግናኝ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ልባችንም ክፉኛ ተሰብሯል፡፡ እኛ ኢትዮጵያዊያኖች ጠላት ያልደፈረን፤ ሰብዓዊ ክብራችንን ያላሳጣን ህዝቦች ሆነን ሳለ በየጊዜው በአካባቢና በማንነት ላይ ያተኮረ እጅግ ዘግናኝና…


