Latest posts

All
amharic
oromifa
somali

Popular

ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ድምፅ ሰጡ
​የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጅሃር በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዛሬው ዕለት በግንባር ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።
በድሬዳዋ አስተዳደር በቀለአድ ክላስተር 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ እየተካሄደ ነው::
የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ ከድር ጁሀር ድምጽ ሰጡ

Significant posts

የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የከተማ ልማት ኮንስትራክሽንና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የድሬዳዋ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣንን ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር የቄራ አገልግሎትን ድርጅትን እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር የፅዳትና ውበት ኤጀንሲ ስር እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ጎበኘ።

Read More

“አካል ጉዳተኞችን አሳታፊና አካታች ለማድረግ ሁሉም ማህበረሰብ የድርሻውን ሊወጣ ይገባዋል”። _ የድሬዳዋ አስተዳደር ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ሃላፊ ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን በዓል ዘንድሮ በአስተዳደራችን ድሬዳዋ አዘጋጅነት “አካታች የፈጠራ ስራና ሽግግራዊ መፍትሔ ለኢትዮጲያ አካል ጉዳተኞች ሁለንተናዊ ተደራሽነት” በሚል መሪ ቃል ለ30ኛ ጊዜ ህዳር 24 ቀን 2015 ዓ.ም ይከበራል።

Read More

የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ከተቋማት ጋር የስራ እቅድ ውል ተፈራረሙ የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት እና የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎች በድሬደዋ አስተዳደር ቻርተር ቁጥር 416/1996 አንቀጽ 12 እና በምክር ቤቱ የአሰራርና የአባላት ስነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 11/2009 መሰረት የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች በአስተዳደሩ ከሚገኙ የአስፈጻሚ ተቋማት ጋር የ2015 ዓ.ም የስራ እቅድ ውል የተፈራረሙ ሲሆን በስራ እቅድ ውል ፊርማው ላይ የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ፈትሂያ አደን፤የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከድር ጁሀር፤ የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎችና የድሬደዋ አስተዳደር የቢሮ ሀላፊዎች ተገኝቷል፡፡

Read More

​የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጅሃር በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዛሬው ዕለት በግንባር ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።

ከንቲባው ድምፃቸውን የሰጡት በአስተዳደሩ ወረዳ 04 በሚገኘው ምርጫ ጣቢያ አንድ ነው። ​ከንቲባ ከድር ጁሃር ድምፅ በሰጡበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዜጎች በሕገ-መንግስቱ የተሰጣቸውን የመምረጥ መብት በአግባቡና በሃላፊነት ስሜት ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አሳስበዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በአገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ዝግጅት መደረጉን የገለጹት ከንቲባው፤ መላው ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥና የአገሪቱን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ…

Read More

የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ አደም ፋራህ ድሬዳዋ ገብተዋል::

ክቡር አቶ አደም ፋራህ ድሬዳዋ የገቡት በሶማሌ ክልል በሽንሌ ከተማ ድምፅ ለመስጠት ነው። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ አደም ፋራህ ድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ፣የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ኢብራሂም ይሱፍ እና የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

Read More