የውል ሰነዱን ያቀረቡት የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት ፅ/ቤት የህግ አወጣጥ ክትትልና ቁጥጥር ሙያዊ ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ቴውዎድስ ባቹሬ ሲሆኑ የውሉ አላማ የምክር ቤቱን እና የምክር ቤቱን ቋሚ ኮሚቴዎች በተቋማት ዓመታዊ እቅዶችና አተገባበራቸው ላይ የሚያደርጉት የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በላቀ ደረጃ ውጤታማ፤ ግልጽነትና ተጠያቂነት የተረጋገጠባቸው ማድረግና አስፈላጊነቱና ጠቀሜታውም ቋሚ ኮሚቴዎች በበጀት ዓመቱ የታቀዱ የተቋማትን ግቦች እና ዋና ዋና ተግባራት ቆጥረው ለመረከብ እና አፈጻጸማቸውን ለመከታተልና ለመቆጣጠር ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡በአጠቃላይ ተቋማት በበጀት ዓመቱ ባቀዱት እና በጸደቀላቸው እቅድ መሰረት የስራ ተፈጻሚነቱና ውጤታማነቱ እንዲረጋገጥ በአስተዳደሩ የልማትና መልካም አስተደዳር ለማስፈን እና ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሆን ሚናውን መጫወት እንደሚገባ በፊርማ ስነስርአቱ ላይ ተገልጿል፡፡
© ም/ቤት ህዝብግንኙነት ክፍል


