የድሬዳዋ አስተዳደር እና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ ለመስራት ተስማሙ፡፡

ስምምነቱ የድሬዳዋ አስተዳደር የስማርት ሲቲ እና ሌሎች የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ አበርክቶዎች ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡
በዚህም የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂን የላቀ አቅም በመጠቀም የከተማ አስተዳደሩን አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የማደርጀት ዘርፈ ብዙ ተግባራት ዉጤታማ ለማድረግ ስምምነቱ አስቻይ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል፡፡
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ኢንጅነር) ባስተላለፉት መልዕክት የከተማ አስተዳደሩ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የታገዙ ለማድረግ ኢንስቲትዩቱ ሁለንተናዊ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር በበኩላቸው ስምምነቱ የድሬዳዋ ከተማን አገልግሎቶች በማዘመን የነዋሪውን ሰላም እና ፀጥታ ከመጠበቅ ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡
© ከንቲባ ጽ/ቤት