የኮሮና ቫይረስን ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንጻር የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሙሉካ መሐመድ እንደተናገሩት በአለም አቀፍ ወረርሽኝ COVID 19 ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ትምህርት ለማስቀጠልና ህፃናት የሚደርስባቸውን ስነ-ልቦናዊ ችግር ለመቅረፍ ትኩረት ተሰቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው በየደረጃው በመሰራቱ የትምህርት ሂደቱ በመጀመሩ ውጤታማ የመማር ማስተማር ሂደትን ከማስፈን አኳያ አቅመ ደካማ ለሆኑ ተማሪዎች እየተደረገ የሚገኘው የቁሳቁስ ድጋፍ አመርቂ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

    እየተደረገ የሚገኘው ጥሩ ምሳሌ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
    የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ እስቂያስ ታፈሰ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት እንደተናገሩት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሌሎች መስኮች ላይ ካሳደረው ተፅዕኖ በተለየ መልኩ በትምህርት ዘርፍ ላይ የፈጠረው ችግር ጉልህ መሆኑን ጠቅሰው የቫይረሱን ስርጭት ከመከላከል አንጻር በአሁን ወቅት የሚስተዋለው መዘናጋት አሰቃቂ በመሆኑ ወላጆች ታዳጊ ህፃናት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
    ድጋፍ ከተደረገላቸው ህፃናት መካከል በተለይ የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው እና በግላኮማ በሽታ ምክንያት ትምህርቷ ላይ ተፅዕኖ ያሳደረባት ተማሪ በማህበሩ የህክምና ወጪ የተሸፈነላት ሲሆን ሌሎች ህፃናትም በተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡