“ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንኳን በደኅና መጡ” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ የእንኳን ደህና መጡ መልእክት አስተላልፈዋል።
    በመልእክታቸውም፣ “ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንኳን በደኅና መጡ። ኢትዮጵያ በሁለት ቀን የሥራ ጉብኝትዎ በደስታ ትቀበልዎታለች።” ብለዋል።
    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ቦሌ አየር ማረፊያ ተገኝተው ለፕሬዚዳንቱ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
    ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ የሚያደርጉ ሲሆን በሚኖራቸው ቆይታ የሁለቱ ሀገራት እና ቀጠናዊ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
    ምንጭ:- ጠ/ሚ/ጽ/ቤት