የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ የተከበሩ ከድር ጆሀር በውጭ ሀገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራዎች፤ እናት ሀገራችን ሰው በፈለገችበት ጊዜ አለንልሽ ብለው፤ የቁርጥ ቀን ልጆች መሆናቸውን በማስመስከር ወደ ቤታቸው መግባት ጀምረዋል። ወንድም-እህቶቼ እንኳን በደህና መጣችሁ። ውቧ እናታችን ድሬዳዋ፤ እንደአቅሟ ለልጆቿ አቀባበል ማጀቷን አሟልታለች። ኑ፤ የናፈቃችሁን የእናታችሁን የፍቅር ማዕድ ተቋደሱ፤ የዘመናት የናፍቆት እንባዋንም አብሱ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#ድሬዳዋ ልጆቿን በናፍቆት እየጠበቀች ነው።


