በከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት 43 ሺህ 610 የአስተዳደራችንን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉ ተገለፀ ።
የሁለተኛው ምእራፍ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔትና ስራ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ-ግብርም በዛሬው እለት ተካሂዷል። የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ከድህነት ወለል በታች የሚኖሩ ወገኖቻችንን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ይታወቃል ከዚሁ ጋር ተያይዞም በድሬዳዋ አስተዳደሩ ይኸው ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምእራፍ ተግባራዊ ከተደረገ ወዲህ በርካታ የአስተዳደሩን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል ። በዛሬው እለትም የሁለተኛው ምእራፍ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔትና ስራ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ተካሂዷል።…


