የባቡር ኢንዱስትሪውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር አ/ማ ፣ የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ እና የድሬደዋ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ የሦስትዮሽ የጋራ የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ፡፡
የጋራ የስምምነት ሰነድ የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ሼር ካንፓኒ ዋና ስራ አስፋፃሚ ዶ/ር አብዲ ዘነበ እንዳሉት ሶስቱ ተቋማት በጋራ መሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈራረማቸው የባቡር ኢንደስትሪውን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሳድገው ገልጸዋል፡፡ በተለይም በባቡር ኢንዱስትሪው የሚፈለገውን የሰው ኃይል ከማፍራት አንፃርና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስፋት ረገድ ሦስቱ ተቋማት በቅንጅት ለመሥራት መስማማታቸው ከሀገራችን አልፎ ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚና በማድረግ…


