ከፀጥታ ሃይሎች ጋር በመቀናጀት የአካባቢያቸውን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆናቸውን የድሬደዋ አስተዳደር ነዋሪዎች ገለጹ፡፡
“ለሀገር ክብር ለክብር እናብር” በሚል መሪ ቃል በድሬደዋ አስተዳደር የተለያዩ ቀበሌ ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሂዷል። በኢትዮ-ጣሊያን ቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ አዳራሽ የተካሄደው ውይይት የመነሻ ፅሁፉ የድሬደዋ አስተዳደር የግብርና መዕድና ኢነርጂ ቢሮ ሀላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ ቀርቧል። በውይይት መነሻ ፅሁፉ መንግስት በኢትዮጵያ የተከሰተውን ችግር በሰላም አማራጭ ለመፍታት በሩ ክፍት መሆኑንና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ…


