የድሬዳዋ አሰተዳደር ም/ከንቲባ እና የንግድ እንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሀርቢ ቡህ የተለያዩ የልማት ፕሮጀግቶችን ተዘዋዉረዉ ጎበኙ

    ክቡር አቶሀርቢ ቡህ ከጎበኛቸዉ ፕሮጀግቶች መካከል በሶስት ኪሎ ከአስፋልት መታጠፊያ በዋሂል ጀሎ በሊና አዲጋ ፈለማ በገንደ ሪጌ አድርጎ ደረቅ ወደብ የሚያገናኝ መንገድ ፣ የመልካ ጅብዱ መንገድ የሚገኝበት ሲሆን ወደ ደረቅ ወደብ የሚያገናኝ በአጠቃላይ 18.78 ኪ/ሜ መንገድ ስራ 22% ላይ የደረሰ መሆኑንና በ2015 ዓ.ም በፌደራል መብግስት በጀት የተያዘለት የመልካ መንገድ እስከ ሰኔ 20/2015 ዓ.ም ድረስ እንደሚጠናቀቅ አቶ ሀርቢ ገልጸዋል።
    በተጨማሪም በድሬዳዋ የምግብ ኮምፕሌክስ በኩል 10.5 km ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ኮሚቴ ተቋቁሞ ስራዎች በየሳምንቱ እየተገመገሙ መፍትሄ እየተሰጠ እንደሚገኝም ሀላፊዉ አብራርተዋል