ወደ ድሬዳዋ ለሚመጡ ዲያስፖራዎች ቀልጣፋ የሆነ አገልግሎት በመስጠት የሀገራችንን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ይቻል ዘንድ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መስራታቸውን በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ባንኮች አስታወቁ ።
የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን ጥሪ ተከትሎ በተለያዩ የአለማችን ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጲያዊያንና ትውልደ ኢትዮጲያዊያን እንዲሁም ደግሞ የኢትዮጲያ ወዳጆች ወደ ሀገራችን ኢትዮጲያ እየገቡ ይገኛሉ ። በድሬዳዋ አስተዳደርም ከ አንድ ሺህ እስከ አንድ ሺህ አምስት መቶ የሚሆኑ ኢትዮጲያዊያንና ትውልደ ኢትዮጲያዊያን ይመጣሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞም በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ባንኮች ለዲያስፖራው ማህበረሰብ አገልግሎት ለመስጠት ይቻል…


