በንጹሃን ላይ የሚፈጸም ግድያ የተሸናፊዎች ድርጊት ነው – ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ
ከሰሞኑ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በንጹሃን ላይ የተፈጸመው ግድያ የተሸናፊዎች ድርጊት ነው ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ። በኦሮሚያ ክልል ሰላምና ፀጥታን ለማረጋገጥ ሰፊ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ÷በፌዴራልና በክልል መንግሥት እየተወሰደ ባለው ኦፕሬሽን አሸባሪ ቡድኖች ጥቃቱን መቋቋም ተስኗቸው ተበታትነዋል ብለዋል። ይሁን እንጅ እነዚህ ተሸናፊ ኃይሎች ሽንፈታቸውን ላለመቀበል የፈሪ ዱላቸውን በንጹሃን ላይ አሳርፈዋል…


