በድሬዳዋ አስተዳደር በጤናው መስክ የሚነሱትን ጥያቄዎች ለመፍታት ዘርፈ-ብዙ ስራዎች በመስራት ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ ።
በድሬዳዋ አስተዳደር በከተማም ሆነ በገጠር በጤናው መስክ መሰራት ያሉባቸውን ስራዎች አስመልክቶ የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው የነበረ ሲሆን እነዚህም ጥያቄዎች በዋናነት የህብረተሰብ ጤና መድህን ተደራሽነት ላይ ያሉ ችግሮች ፣ የመድሀኒትና የህክምና ቁሳቁሶች አቅርቦት ችግር ፣ የቢዮ አዋሌ ጤና ጣቢያ ላይ የሚገኘው የድንገተኛ የቀዶ ህክምና አገልግሎት ከመጀመሩ ጋር ተያይዞ ያለ ችግር ፣ በጤናው ዘርፍ የሰተሰማሩ ሞያተኞች የሙያ ስነ-ምግባርና…


