ከፊታችን ሀምሌ 11 እስከ ሀምሌ 16 2014 ዓ.ም ድረስ በድሬዳዋ አስተዳደር ላይ ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት በተለያዩ መርሀ-ግብሮች በታላቅ ድምቀት የሚከበር ሲሆን በዚህም በአል ላይ ለመካፈል በተለያዩ የአለማችን ሀገራት ላይ የሚኖሩ የድሬዳዋ ተወላጆችና ወዳጆች ወደ ድሬዳዋ በመግባት ላይ ይገኛሉ ።
በዛሬው እለትም ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት ላይ ለመካፈል ከተለያዩ የአለማችን ሀገራት ወደ ትውልድ ከተማቸው ድሬዳዋ ሲገቡ ከፍተኛ የአስተዳደሩ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል ። በቀጣይ ቀናትም በአሉ ላይ ለመታደም ሌሎች እንግዶች ወደ ከተማዋ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።


