የትኛውም መብት ከህግ በላይ ሊሆን አይችልም
የሰው ልጆች መብቶች በመጀመሪያ ከህልውና ጋር በጥብቁ የሚቆራኙ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ የሰው ልጆች በህይወት በመኖራቸው ምክኒያት የሚያስፈልጉ ሌሎችንም ጉዳዮችን ያጠቃልላሉ፡፡ በህገ-መንግስቱ ላይም ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ ተብለው በግልጽ በየፈርጃቸው የተቀመጡ ስለሆነ ማንበቡ ተገቢ ይሆናል፡፡ ሁለቱንም የመብት ዓይነቶች በወንጀል ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ምንም ሳይጎድል እና ሳይሸራረፍ ኢትዮጵያዊ ለሆኑ ዜጎች ሁሉ የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት ያጎናጽፋቸዋል፡፡ ይህን ህገ-መንግስቱ ራሱ ሳያሻማ…


