በድሬዳዋ አስተዳደር የተከሰተውን የቺኩንጉንያ ወረርሽኝ ለመከላከል እየሰራ መሆኑን የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ አስታወቀ
በድሬዳዋ አስተዳደር ለመጀመሪያ ጊዜ የተከሰተውን የቺኩንጉንያ ወረርሽኝ ለመከላከል እየሰራ መሆኑን የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ አስታውቋል። የጤና ቢሮው በዛሬው እለት በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ቺኩንጉንያ የተባለው የበሽታ ምልክት እስካሁን በ3 ሺህ 756 ሰዎች ላይ ተስተውሏል። ሆኖም ግን በሽታው ከወባ እና ከደንጌ ጋር ተመሳሳይነት ስላለው ሁሉም ታማሚዎች ቺኩንጉንያ በተባለው በሽታ ስለመያዛቸው ሙሉ በሙሉ እንዳልተረጋገጠም ነው ቢሮው ያስታወቀው። የድሬዳዋ አስተዳደር…


