ከንቲባ ኢብራሂም ዑስማን ስልጣናቸውን ለምክትል ከንቲባ መሀዲ ጊሬ አስረከቡ
ላለፉት ሶስት አመት ተኩል ድሬዳዋን በከንቲባነት ሲያስተዳድሩ የቆዩት ከንቲባ ኢብራሂም ዑስማን በድርጅታቸው ኢሶህዴፓ ለሌላ ኃላፊነት በመታጨታቸው መንበረ ስልጣናቸውን በገዛ ፍቃዳቸው ለቅቀዋል፡፡ በከንቲባ ማዕረግ ምክትል ከንቲባ ሆነው ድሬዳዋን እንዲያስተዳድሩ የተመረጡት አቶ መሀዲ ጊሬ በ1974 በሽንሌ ሲቲ ዞን የተወለዱ ሲሆን እድገታቸው ድሬዳዋ ላይ እንደሆነ ተነግሮላቸዋል፡፡ ባለ ትዳርና የ 4 ልጆች አባት የሆኑት አቶ መሃዲ በፖለቲካል ሳይንስና አለም…


