ትውልድ ተሻጋሪ አጀንዳዎችን ብቻ ልናስብ እና ልንተግብር ይገባል
ይህች ዓለማችን በርካታ አማራጭ ሀሳቦች በተለያዩ መንገዶች እዚህም እዚያም የሚደመጡባት ናት፡፡ ከእነዚህ አማራጭ አስተሳሰቦች መሀል አንዳንዶቹ በቁጣ ድምጽና በመሳሪያ ታጅበው ሳንፈልጋቸውና ሳናምንባቸው እንድንቀበላቸው የሚያስገድዱ ናቸው፡፡ እነዚህ አስተሳሰቦች የዜጎችን መብቶች ለመጣስና ነጻነትንና ዴሞክራሲን ለማጥፋት እንደተነሱ ገና ከአነሳሳቸው የሚያስታወቁ ናቸው፡፡ ሌሎቹ አማራጨ አስተሳሰቦች ደግሞ በማባበያ እና በሽንገላ ቃላትየታጀቡ፤ በበሬ ወለደ የፈጠራ ወሬ የተሞሉ ሲሆን የዋሆችን የማሳመን አቅማቸው…


