ጦርነት ከፈታው ወሬ የፈታው ይብሳል
ሀገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት በራካታ ዓመታት የውጪና የውስጥ እርስ በእርስ ግጭቶችና ጦርነቶችን አሳልፋለች፡፡ በዚህም ምክኒያት በፖለቲካው፣ በማህበራዊውና በኢኮኖሚው ዘርፍ ትልቅ እመረታ ማምጣት ሲገባት በተቃራኒው ከድጡ ወደ ማጡ እያለች እዚህ ደርሳለች፡፡ የሚገርመውና የሚያሳዝነው ግን አብዛኛዎቹ የውጪም ሆነ የውስጥ እርስ በእርስ ግጭቶች የተከሰቱት በተሳሳቱ ወሬዎችና ሀገራችንን የማተራመስ አጀንዳ ያነገቡ ኃይሎች በሚያቀነባብሩት የሚዲያ ወሬ ድግስ ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከውስጥም…


