የ2011 ዓ.ም የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ተማሪዎች ቅበላ ከጥቅምት 15-18 እንደሚሆን ተገለጸ፡፡

    ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ሲቀበል ከቤተሰብ የተረከበውን አደራ በሙሉ ኃላፊነት ለመወጣት ከአስተዳደሩና ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን እንደሚሰራ ዶ/ር ያሬድ ማሞ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስታውቀዋል፡፡          የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ኡጋዞች፣ አባገዳዎች እንዲሁም የተለያዩ የባለድርሻ አካላት በታደሙበት የውይይት መድረክ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኢብራሂም ኡስማንን ጨምሮ ከሲቲ ዞን አስተዳደርና ከመርመርሳ ጉዳዩይመለከተናል ያሉ የማህበረሰብ ክፍሎች ስለ አካባቢው…

    Read More

      የሴት ካቢኔ አባላቱ ሹመት ለፖለቲካ አመራርነት ተሳትፎ መሰረት ይጥላል

      በድሬዳዋ አስተዳደር የሚኖሩ ነዋሪዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሰሞኑር በተዋቀረው የካቢኔ አባላት 50 በመቶ ሴቶች መሆናቸው ላይ አስተያየት ሰተዋል፡፡ ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ያቀረቡትን 20 የካቢኔ አባላት ሹመት 50 በመቶዎቹ ሴቶች መደረጉ በከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ አመራርነት ተሳትፎ እንዲኖራቸው እየተደረገ ላለው ጥረት መሰረት የሚጥል ብለዋል፡፡…

      Read More

        በድሬ ጉዳይ ላይ ጠያቂ እና ሞጋቾች ልንሆን ይገባል

        በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለው የሠመረ መስተጋብር እንዲቀጥል ሁለቱም በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የሚጠይቁ፣ የሚወያዩ እንዲሁም መፍትሄን በጋራ የሚያፈላልጉ መሆን አለባቸው፡፡ በተለይ ህዝብ የሉዓላዊ ስልጣን ሁሉ ባለቤት በመሆኑ መንግስትን የመከታተል፣ የመደገፍ እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ደግሞ በአግባቡ የመጠየቅ መብትም ባለቤት ነው፡፡ ልማታዊ እና ዴሞክራሲያዊ የሆነ መንግስታዊ ሥርዓት ህዝቡ በሁሉም ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በንቃት የሚሳተፍ ብሎም ጠያቂ…

        Read More

          ነፃነት ሰንደቅ ዓላማ ነፃነት

          ሰንደቅ ዓላማ  የአንድ ሀገርና ህዝብ የነፃናትና የሎዓላዊነት ዓርማ፡፡ ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ብሎ ሲውለበለብ ሰንደቅ ዓላማው የወከለው ሀገርና ህዝብ ነፃና ሉዓላዊ መሆናቸውን የሚያሳይ አስገራሚና የተለየ ስሜት የሚፈጥር ክስተት ነው፡፡ ለዚህም ነው በዓለም መድረኮች አትሌቶቻችን አሸንፈው ሰንደቅ ዓላማችን ከፍ ብሎ ሲውለበለብ እንባቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው የሚያነቡት፡፡ በእነሱ ምክኒያት  በዓለም አደባባይ ሰንደቅ ዓላማው    ከፍ ብሎ መውለብለቡ የፈጠረባቸው ልዩ ስሜት…

          Read More

            የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ስልጠና ፍኖተ-ካርታ ውይይት ተጠናቀቀ

            የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ስልጠና ፍኖተ-ካርታ የጥናት ውጤት ግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት መድረክ በተቋሙ የአስተዳደር ሰራተኞች እና በመምህራን ሰፊ ውይይት ተደርጎበት ተጠናቀቀ፡፡              ከመስከረም 28-30/2011 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው የፍኖተ-ካርታ ውይይት የትምህርት ጥራትና ፍታዊ የትምህርት አሰጣጥ እንዲሁም የነበረው የትምህርት አሰጣጥ ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎል ፡፡ በዩኒቨርሲቲው የማነጅመንት ክፍል መምህር…

            Read More

              በመብራት እና በይዞታ ይገባኛል ጥያቂ ምክንያት የንፁህ መጠጥ ውሀ ፕሮጀክት አለመጠናቀቁ ተገለፀ፡፡

              በአለም ባንክ ድጋፍና በአስተዳደሩ ወጪ ከ5 ዓመት በፊት ስራው የተጀመረው የንፁ መጠጥ ውሀ ፕሮጀክት በመስከረም ወር ወደ ስራ ይገባል ቢባልብ በመብራትና በይዞታ ይገባኛል ችግር ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ስራው መራዘሙ ተገለፀ፡፡የአስተዳደሩ ከንቲባና ከፍተኛ አመራሮች ጨምሮ ፕሮጀክቱን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡  ከአለም ባንክ በተገኘ ድጋፍ እና በአስተዳደሩ ወጪ ሰባት መቶ ሚሊየን ብር በጀት የተያዘለት ይህ ፕሮጀክት የንፁህ መጠጥ ውሀ…

              Read More

                የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምስራቅ ዲስትሪክት ለ7ኛ ዙር የይቆጥቡ ይሸለሙ ባለእድለኞችን ሸልሟል፡፡

                በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል ያለው የቁጠባ ባህል እንዲጎለብት በተለያዩ መንገዶች በሰራሁት ስራ ከ1.2 ሚሊየን በላይ ደንበኞችን ማፍራት አስችሎኛል አለ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምስራቅ ዲስትሪክ፡፡ ባንኩ የ7ኛው ዙር የይቆጥቡ ይሸለሙ ባለእድለኞችን ሸልሟል፡፡ ወጣት ናትናኤል ሁነኛው በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ የመንግስት ሰራተኛ ሲሆን ከእለት ገቢው ላይ በቆጠባት አነስተኛ ገንዘብ በደረሰው እጣ መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ተሸላሚ ሆኗል ወጣቱ…

                Read More

                  የበጐ ፍቃደኝነት ስራ ማብቂያ የለውም ሲሉ የአስተዳደሩ ወጣቶች ገለፁ ለ25 በጐ ፍቃደኞችም እውቅና ተሰጥቷል፡፡

                  የድሬደዋ አስተዳደር የ2010 ዓ.ም የክረምት ወራት የወጣቶች በጐ ፍቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ ስነ-ስርዓት በከተማና ገጠር ቀበሌ የተውጣጡ በጐፍቃደኛ ወጣቶች በተገኙበት ተጠናቅቋል፡፡ በመዝጊያ ስነ-ስርዓቱላይ በገንዘብና በጉልበታቸው ድጋፍ ላደረጉ የተለያዩ አካላትና ተቋማት ምስጋናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ የአስተዳደሩን ከንቲባ በመወከል ንግግር ያደረጉት የኢህአዴግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሽመልስ ከበደ እንደተናገሩት በአስተዳደራችን የወጣቶች የክረምት በጐ ፍቃድ አገልግሎት ላይ ሰላሳ ዘጠኝ ሚሊዮን ስድስት…

                  Read More

                    የትምህርት ጉዳይ የባለድርሻ አካላት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ህብረተሰብ ነው ያሉት የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ያሬድ ማሞ

                    የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ስልጠና ፍኖተ-ካርታ የጥናት ውጤት ግብዓት ማሰባሰቢያ የውይይት መድረክ እየተካሄድ ይገኛል፡፡ ከመስከረም 28-30/2011 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው የፍኖተ-ካርታ ውይይት የትምህርት ጥራትና ፍታዊ የትምህርት አሰጣጥ እንዲሁም የነበረው የትምህርት አሰጣጥ ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ያሬድ ማሞ እንደተናገሩት የትምህርት ጉዳይ የባለድርሻ አካላት…

                    Read More

                      ብዙ ዋጋ ከፍለን የደከምንበትን ጉዳይ ማን ይረከብ?

                      የአስተዳደሩ መልዕከት ብዙ ዋጋ ከፍለን የደከምንበትን ጉዳይ ማን ይረከብ? ሀገር የሚገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ እንጂ በአንድ ትውልድ ብቻ ተገንብቶ ያለቀለት ሀገር በዚህ ምድር ላይ የትም አይገኝም፡፡ ስለሆነም ካለፈው ትውልድ ያለው ትውልድ ያላለቀ ሥራን እየተረከበና ከውድቀታቸውና ከስኬታቸው እየተማረ ሁሉም በተራው አደራውን ሲወጣ ነው ሀገር እዚህ የደረሰችው፡፡ ይህ የአደራ ቅብብሎሽ ትላንትናም ነበር ዛሬም አለ ነገም ይቀጥላል፡፡ በዚህ ሁሉ…

                      Read More