ድሬዳዋ ለጅቡቲ ወደብ ቅርብ እንደመሆኗ የኮረና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ተባለ
የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ለምለም በዛብህ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በድሬዳዋ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል፡፡ የማህበረሰቡን ለኮረና ቫይረስ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚያግዝ የግንዘቤ ማስጨበጥ ተግባርም በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ወ/ሮ ለምለም ገልጸዋል ፡፡ ድሬዳዋ ለጅቡቲ ወደብ ቅርብ እንደመሆኗ ከጅቡቲ ለሚገቡ ዜጎች የለይቶ ማቆያና ህክምና ዋና ማዕከል ሆኖ በማገልገል ላይ…


