የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት በከተማው ከሚገኙ ባሀለብት አቶ ሰኢዶ ሀሰን ጋር በመተባበር በበጎ ፍቃድ የአረጋውያን ቤት እድሳት ያስገነባውን ቤት አጠናቆ በዛሬው እለት ለባለቤቶቹ አስረክቧል::

በዚህም በርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን በመገኘት ለባለቤቶቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት በማስተላለፍ፤ አቅመ ደካማ ወገኖችን በርብርብ ማገዝ ከፍተኛ የሆነ የህሊና እርካታ እንዳለው ገልፀዋል። አቶ ገበየሁ አያይዘውም ቤቱ በጥራትና በፍጥነት ታድሶ መጠናቀቁን ጠቁመው ሁሉም የእርስ በእርስ መረዳዳት ባህልን ማዳበር ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ቤት የተገነባላቸው አቅመ ደካማ ወገኖች በበኩላቸው…

Read More

የከተማችን አሽከርካሪዎች አመታዊውን የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በአል ለማክበር ወደ ከተማችን ሚመጡ እንግዶች በጥሩ ስነምግባር እና በተቀመጠው ታሪፍ ብቻ ሊያገለግሉ እንደሚገባ ተጠቆመ።

በአስተዳደሩ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን የመንገድ ደህነነት እና መድህን ፈንድ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ይህነኑ ለመቆጣጠር በሙሉ አቅሙ ባለሙያዎቹን አሰማርቶ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል። የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር ኢንጅነር ሁሴን ጀማል በከተማ መውጫ ደንገጎ መስመር እንደሁም ትናንት ማምሻ በኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ጣቢያ የድሬደዋ ጣቢያ በመገኘት የታሪፍ ቁጥጥር ሂደቱን ተመልክተዋል። ከመልካጀብዱ ፖሊስ ጣቢያ ጋር በመቀናጀት በጣቢያው ለሚገኙ የታክሲ ማህበር አባላት ግንዛቤ…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ለቁልቢ ገብርኤል አመታዊ የንግስ በአል ድሬዳዋ ለገቡት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የእንኳን ደህና መጡ መልዕት በማስተላለፍ ስጦታ አበርክተውላቸዋል።

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፈረንጆችን የገና በዓል ለሚያከብሩ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመላው ዓለም የፈረንጆችን የገና በዓል ለሚያከብሩ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዓሉን ለሚያከብሩ በሙሉ፣ ለኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ወዳጆች፣ የዳያስፖራ ማኅበረሰብ እና የዓለም ቤተሰብ መልካም የገና በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ብለዋል። በዓሉ የደስታ፣ የሰላም እና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን በኤክስ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል።

Read More