በኢፌድሪ አየር ኃይሉ የምስራቅ አየር ምድብ 8ኛውን የመከላከያ ቀን በዓል አስመልክቶ የተዘጋጀ ስፖርታዊ ውድድሮች ፈፃሚያቸውን አግኝተዋል፡፡

    በውድድሩ የእግር ኳስ ጨዋታ የገመድ ጉተታን ጨምሮ የተለያዩ አዝናኝ ስፖርታዊ ፉክክሮች ተከናውነዋል፡፡

    በአየር ምድቡ እንደዚህ አይነት ስፖርታዊ ውድድሮች መካሄዳቸው ውስጣዊ አንድነት ከማጠናከር ባለፈ ተልዕኮውን በብቃት የሚወጣ ሰራዊት እንዲገነባ አስተዋፅኦ የጎላ መሆኑን በኢፌድሪ አየር ኃይል ምስራቅ አየር ምድብ ዋና አዛዥ ኮሮኔል አበበ ለገሰ ተናግረዋል፡፡