የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከዲር ጁሐር የድሬዳዋ ስታዲየም በአዲስ መልክ ተገንብቶ የፊፋ ደረጃን በማሟላቱ ሂደት የበኩላቸውን ድርሻ ላደረጉትና ለተረባረቡት ሁሉ እንዲህ በማለት በማህበራዊ ሚዲያ የትስስር ገፃቸው ምስጋናቸውን አቅርቧል …

አንጋፋውን የድሬዳዋ ስታዲየም፥ የፊፋን ደረጃ ያሟላ የሰው ሰራሽ ሣር ሜዳ ባለቤት በማድረግ ሂደት ውስጥ፥ አስተዋፅኦ የነበራችሁ ግለሰብ እና ተቋማት በሙሉ ክብር ይገባችኋል።

ከሁሉም በላይ ግን… ይህ ስኬት እውን እንዲሆን የተሰጠውን ትልቅ ሀላፊነት በብቃት ለተወጣው፥ ለምወደው ወንድሜ ፉአድ ኢብራሂም ያለኝ ልባዊ ምስጋና ከቃላት በላይ ስለሆነ፥ የአስተዳደራችን ነዋሪዎች እንድትመርቁት በክብር እጠይቃለሁ። አለም አቀፉ ስታዲየማችንን ለድሬዎች ሀብት፥ ለኢትዮጵያውያን ደግሞ ኩራት የማድረግ ጉዟችን ይቀጥላል። በርቱ እንበረታለን!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *