በድሬዳዋ አስተዳደር የወረዳ 3 የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑ እህት ወንድሞች በቅድስት ማሪያም ካቴደራል ቤተክርስትያን በመገኘት የፀሎተ ሀሙስን ስነ-ስርአት አከናውነው ለወጡ የእምነቱ ተከታዮች የታሸጉ ውሀዎችን እና ድፎዳቦ የመስጠት መርሀ-ግብር በዛሬው እለት አካሄዱ ።

በመርሀ ግብሩ ላይ ያነጋገርናቸው የእስልምና እምነት ተከታይ እህት ወንድሞች የዛሬው ፕሮግራሞችን እንደሁሌውም ፍቅራችንን እና አብሮነታችንን ለማሳየት ያዘጋጀነው ነው በማለት ተናግረዋል።

አስተባባሪዎቹ አያይዘውም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *