ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 36ኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ነው፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ ቢሰጥባቸው ያሏቸውን ጥያቄዎችና አስተያየቶችን እያቀረቡ ይገኛል፡፡
ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከልም፡-
• የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጻም በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝና፤ ለስምምነቱ መፈፀም መንግስት ከባለድርሻ አካለት ጋር እያከናወናቸው ያሉ ስራዎች?
• በኮሪደር ልማቱ በታቀፉ አካባቢዎች በዝቅተኛ የንግድ ስራዎች ላይ የተሰማሩ ዜጎች ለከፋ ችግር እንዳይዳረጉ እና በተሻለ ሁኔታ ለማቋቋም ምን እየተሰራ ነው፤ የኮሪደር ልማቱ ወደ ሌሎች ክልሎች እንዲስፋፋስ ምን ታቅዷል?
• የኢትዮጵያ አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታ በዋና ዋና አመላካቾች ምን ደረጃ ላይ ነው ?
• የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ንረትን ከመቀነስ አንጻር እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ህይወት ለማሻሻል መንግስት ምን አቅዶ እየሰራ ነው?
• በሀገሪቱ በአርብቶ አደሮችና አርሶ አደሮች አከባቢዎች እተከሰቱ ያሉ የተለያዩ ወረርሽኞችንና በሽታዎችን ለመቀነስ ምን እየተከናወነ ነው?
• ማንኛውም የመንግስት አገልግሎት የሚገኘው በእጅ መንሻ ሆኗል፤ ታዲያ መንስግት ይህን ለመፍታት ምን እየሰራ ነው? በጥቅሉ የመንግስታዊ ሌብነት እና የሙስና ችግሮችን ለመፍታት ምን ታቅዷል?
• በቅርቡ ከቀረበው የኦዲት ሪፖርት ጋር ተያያዞ ብዙ ተቋማት የሃብት ብክነት እየታየባቸው ነው፤ መንግስት ይህን ከመፍታት አንጻር ምን እየሰራ ነው?
• የአዋሽ ኮምቦልቻ ሀራ ገበያ የባቡር መንገድ ከመልሶ ግንባታ አኳያ ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?
• በትግራይ፣ በአፋር እና በአማራ ክልሎች የመልሶ ማቋቋም ስራዎች በምን ደረጃ ላይ ይገኛሉ የሚሉና ሌሎች ማብራሪያና ምላሽ ያስፈልጋቸዋል ያሏቸውን ጥያቄዎች የምክር ቤቱ አባላት በማቅረብ ላይ ይገኛሉ፡፡


