ለ19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን አስተዋፆ ላበረከቱ ክልሎች ለድሬደዋ አስተዳደር እና ለአዲስአበባ ከተማ መስተዳድር የእዉቅና ፣ምስጋና የዕራት ግብዣ መርሀግብር ተካሄደ ።

19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች በዓል በደማቅ ሁኔታ ለተከታታይ 4ቀናት በተለያዩ መርሀግብሮች እንዲከበር አስተዋፆ ላበረከቱት የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የተዘጋጀላቸውን ሽልማት እና ምስጋና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ጥላሁን ከበደ እጅ ተረክበዋል።

የኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶታገሰ ጫፎ የኢፌድሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የክልል ርዕሳነ መስተዳዳድሮች እና የሁለቱ ከተማ መስተዳድር በተገኙበት የእራት ምሽት ተካሂዷል ።

19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች በአልን ያዘጋጀው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት አፈጉባኤ ክብርት ፈቲህያ አደን የተዘጋጀላቸውን ሽልማት አስረክቧል።

የ11 ክልል አፈጉባኤዎች የተዘጋጀላቸውን ሽልማት ከክልሉ አፈጉባኤ እጅ የተረከቡ ሲሆን በነገው እለትም በሚካሄደው ማጠቃለያ መርሐግብር የሚጠናቅ ይሆናል።

Diretv – አማርኛ

ምስል:- ናትናኤል ገ/ዮሃንስ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *