የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እና ተጠሪ ተቋማት ፀረ-ሙስና ቀንን ምክንያት በማድረግ ውይይት አካሄዱ::
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን ባስተላለፉት መልዕክት ሙስና የአስተዳደር ስርዓትን የሚሸረሽር፣ የህዝብ አመኔታን የሚንድ እና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገትን የሚያደናቅፍ መሆኑን አንስተዋል፡፡ 21ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ=ሙስና ቀን ‘”ከወጣቶች ጋር በመተባበር ሙስናን መከላከል፤ የነገን ስብዕና ለመቅረጽ“ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ሲሆን መሪ ቃሉ ለበዓሉ የተመረጠበት ምክንያት ሙስና ያለልዩነት…


