ህብረተሰቡ ግብሩን በአግባቡ እንዲከፍል የሀይማኖት አባቶች ጥሪ አቀረቡ
በድሬደዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን በተከናወነው የታክስ ንቅናቄ መድረክ ተገኝተው ለንግዱ ማህበረሰብ ግብርን በአግባቡ አለመክፈል በምድርም በሰማይም እንደሚያስጠይቅ ያስተማሩት የሀይማኖት አባቶች ግብርን በመክፈል ሁሉም ዜጋ ለሀገሪቱ እድገት አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ከሐምሌ 1 እስከ ሐምሌ 30 የደረጃ 3 (ሐ) ግብር ከፋዮች ግብራቸውን የሚከፍሉበት ወቅት በመሆኑ ሁሉም ግብር ከፋይ በወቅቱ ግብሩን እንዲከፍል ያሣሠቡት የድሬደዋ አስተዳደር ገቢዎች…


