ፋሲካን ስናከብር ፍቅርን በተግባር በማሳየት እንዲሆን የሃይማኖት አባቶች መከሩ ህዝበ ክርስቲያኑ ማህበራዊ እሴቶችን ለመታደግ ላደረገው ርብርብ ምስጋና ተችሮታል፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር የፋሲካ በዓል በልዩ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ዋና አዘጋጅነት በተዘጋጀው ልዩ የበዓል ፕሮግራም ላይ የተገኙት የሃይማኖት አባቶችም ለነዋሪው ህዝብ የፋሲካ በአል ሲከበር ክርስቶስ ለሰው ልጆች የከፈለውን መስዋትነት በማሰብ ፍቅርን በተግባር በማሳየት ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የሃይማኖት አባቶቹ ባስተላለፉት የጋራ መልዕክት የፋሲካ በዓል ታላቅ ፍቅር የታየበት እንደመሆኑ መጠን በዓሉን…


