ከንቲባው ከድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር ከድር ጁሃር በስልክ ባደረጉት ግንኙነት የተፈጠረው የእሳት ቃጠሎ ከልባቸው እንዳዘኑና በቀጣይ ከአስተዳደሩ ጎን እንደሚቆሙ አረጋግጠውላቸዋል፡፡
ከንቲባ አቶ ሰኢድ ዳውድ በስልክ መልዕክታቸው ‘’በድሬዳዋ ላይ ስለደረሰው የእሳት ቃጠሎ በመስማቴ በጣም አዝኛለሁ ፣ በዚህ አሳዛኝ ወቅት የጅቡቲ ከተማ አስተዳደር እና የጅቡቲ ዋና ከተማ ህዝብ ከጎናቹ መሆናችንን ልገልፅልህ እወዳለሁ” ብለዋል፡፡
አቶ ሰኢድ ዳውድ አክለውም በዚህ አሳዛኝ ሁኔታ የተጎዱት ከድሬዳዋ እህት ህዝብ ጋር ችግሩንና ጉዳታቸውን እንካፍላለን በዚህው አጋጣሚ አላህ የሰውን ህይወት ይጠብቅልን ብለዋል፡፡


