ኢትዮጵያ በታምራት ቶላ አማካይነት የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ ዛሬ በተካሄደው የወንዶች የማራቶን ውድድር አትሌት ታምራት ቶላ 1ኛ በመውጣት ለሀገሩ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል።

ከ2 ዓመታት በፊት በአሜሪካ ኢዩጂን በተደረገው የዓለም ሻምፒዮና የርቀቱ አሸናፊ የነበረው ታምራት፤ ከ21 ኪሎ ሜትር ጀምሮ ውድድሩን በልዩነት እየመራ በማጠናቀቅ ነው የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *