በዚህም በመድረኩ ከሰባቱም የእምነት ተቋማት የተውጣጡ እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል።
በኦረንቴሽኑ ወቅት ያነጋገርናቸው ወጣቶችም የሀይማኖት ተቋማት ስለ አንድነት፣ ስለ ሰላም እና ህብረት ሁሌም እያስተማሩ እንደሚገኙ አንስተው፤ እኛ ወጣቶችም የድሬዳዋን ሰላምና አብሮነት እንደ ሁሌውም አጠናክረን የማስቀጠል ሀላፊነት አለብን ሲሉ ተናግረዋል።
ድሬዳዋ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሰላም ኮንፍረንስ ሊዘጋጅባት መሆኑ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ተሳታፊዎቹ አያይዘው ገልፀዋል።
በመጨረሻም ወጣቶቹ ኮንፍረንሱ ላይ ለመታደም የሚመጡ እንግዶችን በተለመደው የድሬዳዋ ፍቅር ተቀብለን ለማስተናገድ ዝግጁ ነን ሲሉ አመላክተዋል።
በኤደን ሳሙኤል
ፎቶ:-ሰላም አበበ


