በአስተዳደራችን በሚገኙ ት/ቤቶች “እንድናገለግልዎ ማስክዎን ያድርጉ” በሚል መሪ ቃል ተማሪዎችንና የት/ቤት ማህበርሰቡን ያሳተፈ ንቅናቄ በምስራቅ ጀግኖች ት/ቤት ተጀመረ::

    ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የጤና ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ለምለም በዛብህና የት/ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሙሉካ መሃመድ ሲሆኑ ተማሪዎች ኮሮናን ለመከላከል የሚደረጉ የጥንቃቃቄ ተግባራትን በሚገባ እንዲተገብሩና የገፅ ለገፅ ትምህርት በበሽታው ስርጭት መስፋፋት ዳግም እንዳይቁዋረጥ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል::
    ተማሪዎች በት/ቤትና ከቤት ውጭ ባላቸው እንቅስቃሴዎች ሁሉ ማስክ በመልበስ፣ የእጃቸውን ንፅህና በመጠበቅና አካላዊ ርቀታቸውን በመጠበቅ ራሳቸውንና ሌሎችን ከበሽታው እንዲታደጉም ሀላፊዎቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል::
    ከፕሮግራሙ በይፋ መጀመር በኃላም ተማሪዎችና የት/ቤቱ ማህበረሰብ በት/ቤቱ ዙሪያ ባሉ ቦታዎች በመዘዋወር ለማህበረሰቡ የጥንቃቄ መልዕክቶችን የማስተላለፍ ስራ ሰርተዋል::
    የንቅናቄ ፕሮግራሙ በቀጣይ በሁሉም ት/ቤቶች የሚካሄድ ይሆናል::
    ምንጭ : ድሬዳዋ ጤና ቢሮ