Headlines

    በድሬደዋ አስተዳደር በትላንትናው ዕለትም በተወሰኑ ቀበሌዎች ግጭት እንደነበር ተገለፀ

    ባለፉት ቀናት በድሬደዋ የተከሠተው ግጭትበ12/2011ዓ.ም ዕለትም በቀበሌ 06፣07፣08፣09 ከምሽት 1 ሠዓት እስከ ምሽቱ 5 ድረስ የቆየ መንገድ መዝጋት ውከት እንደነበር የአስተዳደሩ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ አቶ እስቅያስ ታፈሰ ገልፀዋል፡፡ ከምሽቱ አንድ ሠአት በተጀመረው ግጭትም የአንድ ሰው ህይወት ማለፍንና አንድ ሰው ከባድ አደጋ ደርሶበት በድል ጮራ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንደሚገኝ ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ በለገሀሬ አንድ ቤት…

    Read More

      ሴቶች የማህበረሰብ ድርሻቸውን በሚገባ ሊወጡ ይገባል

      ሴቶች በማህበረሰቡ መሀል ያላቸው የመምራት ኃላፊነት ድርሻ ድርብ እና ከፍተኛ ነው፡፡ ይህ ኃላፊነት የሚጀምረው የሀገር እና የህዝብ መሠረት የሆነው ቤተሰብ ውስጥ ነው፡፡ ቤተሰብን መምራት ምን ያህል አንደሚከብድ የሚታወቀው በሆነ አጋጣሚ የቤተሰብ አስተዳዳሪ የሆኑት ሴቶች ከቤተሰብ ተለይተው ሲቆዩ ነው፡፡ ለዚህ ዋና እማኝ የሚሆኑት ሁኔታው ያጋጠማቸው አባወራዎች ናቸው፡፡ የሴቶች የመምራትና የኃላፊነት ድርሻ በቤተሰብ ውስጥ ብቻ የተወሰነ አይደለም፡፡…

      Read More

        መብቶቻችንን በህጋዊ እና ህጋዊ መንገድ ብቻ ልንጠቀም ይገባል

        ሥርዓቶች ቢፈራረቁም አፈናውና ጭቆናው ባንገፈገፈው የብሄረሰቦች ስብስብ የተራዘመና ብዙ መስዋዕትነት በጠየቀ መራራ ትግል ዕውን የሆነው ሕገ-መንግስታችን በርካታ መብቶችን አጎናጽፎናል፡፡ እነዚህ መብቶቻችን በማያሻማ መልኩ በሁለት መሠረታዊ የመብት ዓይነቶች በግልጽ ተቀምጠዋል፡፡ እነዚህ የመብቶቻችን ዓይነቶች ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በመባል ይታወቃሉ፡፡ ሰብዓዊ መብቶቻችን ሰው ሆነን በመፈጠራችን ብቻ የምንጎናጸፋቸውና በማንም ፍቃደኝነት የማይሰጡን እንዲሁም የማይወሰዱብን መብቶቻችን እንደሆኑ ህገ-መንግስታችን ያሰረዳል፡፡ ይህን…

        Read More

          ነገን የተሻለ ለማድረግ ወጣቱ ግንባር ቀደም ሚናውን ሊጫወት ይገባል

          የወጣትነት ዕድሜ ችኩልነት፣ ለአዳዲስ ነገሮች መጓጓት እና ሁሉን ነገር ደፍሮ በተግባር ለማየት የሚፈለግብት ዕድሜ ነው፡፡ እነዚህ የወጣትንት ዕድሜ መገለጫ ባህሪያት በአግባቡ ተገርተው ጥቅም ላይ ካልዋሉ የራሳቸው ጎጂ ጎን አላቸው፡፡ በዚህ ዕድሜ በችኮላ የሚወሰኑና የሚደረጉ ተግባራት ሁሉ ፍጻሜያቸው የዕድሜ ልክ ጸጸት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ከዛሬ አልፎ ነገን አሻግሮ በማየት ሰከን ብሎ መወሰን እና ውሳኔን…

          Read More

            ለዘመናት ዋጋ ከፍለን የደከምንበትን የሀገር ጉዳይ ማን ይረከብ ?

            ሀገር የሚገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ እንጂ በአንድ ትውልድ ብቻ ተገንብቶ ያለቀለት ሀገር በዚህ ምድር ላይ የትም አይገኝም፡፡ ስለሆነም ካለፈው ትውልድ ያለው ትውልድ ያላለቀ የሀገር ሥራን እየተረከበና ከውድቀታቸውና ከስኬታቸው እየተማረ ሁሉም በተራው አደራውን ሲወጣ ነው ሀገር እዚህ የደረሰችው፡፡ ልብ ልንለው የሚገባው ሁሉም በየተራው የደከመው ግን አንዲት መተኪያ የሌላትን ሀገር ለመገንባት ነው፡፡ ባለአደራው ትውልድ መክፍል የሚገባውን ዋጋ ሁሉ…

            Read More

              ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ጌጠኛ ድንጋይ መንገዶች እየተገነቡ ናቸው

              ድሬዳዋን ማህበራዊና ምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴውን የሚያጎለብቱ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በወጣባቸውየጌጠኛ ጡብ ድንጋይ መንገዶች እየተገነቡ መሆናቸውን የከተማው ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ገለፀ፡፡      በአብዛኛው ተጠናቀው አገልግሎት የጀመሩት መንገዶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ማህበራዊ ኑሮን በማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የመንገዱ ተጠቃዎችና ገንቢዎች ተናግረዋል፡፡      የድሬዳዋ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የልማት ዕቅድ አስተባባሪ አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ እንደገለፁት…

              Read More

                ፀረ ሰላም ኃሎችን ከብሄርና ከሐይማኖት ተቋማት ልንለያቸው ይገባል

                ከሦስት አሥርተ ዓመታት በላይ የብሄር ብሄረሰቦችና የሌሎችም ልዩነቶች  የእኩልነት  ጥያቄ  በህግ መንግስቱ ከተመለሰ በኋላ እንኳን ልዩነቶቹን እንደ መደበቂያ ምሽግ የመጠቀም ስትራቴጂ ቀጥሏል፡፡ በተለይ በተለይ ያኮረፉ ፖለቲከኞች፣ ኪራይ ሰብሳቢዎች፣ ሽብርተኞችና ሌሎችም ጸረ ሠላም ኃይሎች ለሁሉም ዜጎች የተዘረጋው ሠላማዊውና ህጋዊው መንግድ አላዋጣ ሲላቸው ህገ ወጡን መንገድ ለመጠቀም እንደ ምሽግ የሚጠቀሙት ሐይማኖትንና ብሄርን ነው፡፡    ይህን አካሄዳቸውን አደገኛ…

                Read More

                  ለውጡ ያመጣውን ጥሩ ዕድል ልንጠቀምበት ይገባል

                  በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለፈውን የሀገራችንን ነባራዊ ሁኔታ በቅጤ ያገናዘበ እና ብልሀት የተሞላበት የለውጥ አቅጠጫ መከተል የጀመርነው አሁን ነው፡፡ ይህን አዲሱን የለውጥ ጉዞ ለየት የሚያደርገው መንግስት ኃይልን  የመጠቀም አቅሙና ዕድሉ እያለው እሱ አያስፈልግም በማለት በፍቅርና በይቅርታ እንደመር  ብሎ በውጪም በውስጥም ላሉት ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ጥሪ ያቀረበበት የለውጥ ጉዞ መሆኑ ነው፡፡             ከዚህ በፊት  ሀገሪቱን የመምራት ዕድል…

                  Read More

                    ለውጡን የማስቀጠል እና ያለማስቀጠል ጉዳይ

                    በዚህ ትውልድ ፊት የተደቀነው የቤት ሥራ በእጅጉ ከባድ እና መስዋዕትነት የሚያስከፍል ቢሆንም የቤት ሥራውን የመወጣትና ያለመወጣት  ጉዳይ ግን የህልውና ጉዳይ ነው፡፡ በሀገር ደረጃ የተጀመረው በፍቅርና በይቅርታ የመደመር ጉዞ ለውጥ ገና ከጅምሩ እንቅፋቶች እና ተግዳሮቶች የበዙበት ቢሆንም ከሀገር ውስጥ እስከ ዲያስፖራ ከዛም አልፎ ጎረቤት ሀገሮችን ሳይቀር በርካቶችን ከጎኑ ለማሰለፍ ችሏል፡፡        የለውጥ ጉዞውን አሁን የጀመርነው ከበርካታ…

                    Read More

                      ዓለም የቱሪዝም ቀን በድሬደዋ አስተዳደር በተለያዩ ዝግጅት ተከበረ

                      የቱሪስት መዳረሻዎችን በአግባቡ በማልማት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡ የአስተዳደሩ ንግድና ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤጽ   ዓለም የቱሪዝም ቀን ‹‹ ዲጅታል ትራንስፎርሜሽን ለቱሪዝም እድገት››በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል፡፡ ዓለምአቀፍየቱሪዝምቀንበሀገር አቀፍ ደረጃ ለ39 ጊዜ በሀገራችን ለ31ኛ ጊዜ የተከበረ ሲሆን በድሬደዋ አስተዳደርም ከጥቅምት 8-10/2011 ዓ.ም ዓለም የቱሪዝም ቀን የከተማ ፅዳት ፣በፎቶ ኤግዝቨሽን ፣የተለያዩ የቱሪስት…

                      Read More