ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመስከረም እና ጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም በመሠረተ ልማት፣ በገጠር ልማት፣ በአስተዳደራዊ ማሻሻያ እና በዲፕሎማሲያዊ ትብብር ላይ ያተኮሩ ተከታታይ አገራዊ እና ዓለም አቀፍ ተግባራትን አከናውነዋል። ያለፈውን ወር ተግበራት በጨረፍታ እነሆ፥
የከተማ ልማት እና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ከዳንጎቴ ግሩፕ ጋር በመተባበር ለሚገነባው የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ እና በጎልደን ኮንኮርድ ግሩፕ አማካኝነት ለሚገነባው የጎዴ ነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ መሠረት መጣላቸው ከካናወኗቸው ቀዳሚ ተግባራት የሚጠቀሱ ናቸው። የጎዴ ነዳጅ ማጣሪያ ከሂላል የነዳጅ ስፍራ ድፍድፍ ነዳጅ በማውጣት፣ በማጣራትና በማጠራቀም በዓመት 3.5 ሚሊዮን ቶን…


