Itiyoophiyaatti Ambaasaaddarri Faransaay Kabajamoo Aleeksiis Laameek gara ‘Itiyoophiyaa Xiqqoo’ Dirree teenyaa dhufuu isaaniitiin Onneerraa gammachuu guddaatu ​​natti dhaga’ama.

Daawwannaan hojii kun, waamicha kanaan dura Kabajamoo Ministirri Muummee Abiy Ahimad (PhD), Pirezidaanti biyya Faransaay Maakrooniif akka gara Itiyoophiyaa dhufanii Inveestii godhaniif jecha afeerraa dhiheeysanifitti aanuudhaan kan gaggeefame Daawwiin hujii kun, Hariiroo seena-qabeessa ta’e kan yeroo dheeraadhaaf Dirree Dhawaa fi biyya Faransaay jidduu jiru daran kan cimsuudha. Turtii walgahii kan Garee Miseensoota inveestimantii 16 qabuufii…

Read More

በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አንባሳደር አሌክስ ላሜክ የተመራ ልዑካን ቡድን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ድሬዳዋ ከተማ ገባ

ልዑኩ ከድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ጋር እንዲሁም ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በማህበራዊ ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በዲፕሎማሲው መስክ ስራዎችን በተጠናከረ መልኩ መስራት በሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ምክክር የሚያደርግ ይሆናል። ልዑኩ ድሬዳዋ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ በክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አደን፣ በድሬዳዋ አስተዳደር…

Read More

ፈረንሳይ እና ድሬዳዋ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መስኮች ስራዎችን በጋራ አጠናክረው እንደሚሰሩ አስታወቁ

የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አንባሳደር አሌክስ ላሜክ ከተመራ ልዑካን ቡድን ጋር በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መስኮች ስራዎችን በጋራ አጠናክሮ ለመስራት በሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ተወያይተዋል። በዚህም በመድረኩ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ለእንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን በማስተላለፍ፤ ድሬዳዋ ቀንም ለሊትም እንቅስቃሴ ያላት ሰላማዊ ከተማ…

Read More

የሲንጋፖር ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግን በክብር ተቀብያለው።

ውይይታችን በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለንን ግንኙነት ለጋራ ነጋችን ወሳኝ በሆኑ መስኮች በጋራ ለመሥራት በምናደርገው ጥረት ውስጥ አንድ ጠቃሚ ርምጃ ነው። በተለይም በክሂሎት ልማት እና የካርበን ብድር ትብብር ላይ ያደረግናቸው የመግባቢያ ስምምነቶች ጽኑ እና ለነገው ገበያ ዝግጁ የሆኑ ሠራተኞችን ለማፍራት ብሎም በአየር ንብረት ጥበቃ ረገድ ዘላቂ፣ ዝቅተኛ ካርበን የሚያወጣ እድገት ለማረጋገጥ ያለንን የጋራ አቋም የሚያንፀባርቅ ነው።…

Read More

በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር የሆኑት ክቡር አሌክሲስ ላሜክ፥ ወደ ‘ትንሿ ኢትዮጵያ’ ድሬ በመምጣታቸው ከልብ ደስ ብሎኛል።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዚህ ቀደም፥ በኢትዮጵያ ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ለፕሬዝዳንት ማክሮን ያቀረቡትን ግብዣ ተከትሎ የተደረገው ይህ የሥራ ጉብኝት፥ ታሪካዊውን የድሬዳዋ እና የፈረንሳይ ግንኙነት በይበልጥ የሚያጠናክር ነው። 16 የኢንቨስትመንት ቡድን አባላትን ከያዘውና በአምባሳደር ላሜክ ከተመራው ልዑክ ጋር በነበረን ቆይታ የእህትትማማች ከተሞችን ግንኙነት ለማሳደግ፥ በባህል እና ቱሪዝም መስኮች ድጋፍ ለማድረግ፥ እንዲሁም የፈረንሳይ ባለሀብቶች በአስተዳደራችን…

Read More

የኢፌዴሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ የድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ እና የኮሪደር ልማት ግንባታን ጎበኙ

#DGC ህዳር 15/2018 የኢፌዴሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ በድሬዳዋ አስተዳደር ተገንብቶ በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት እየሰጠ ያለው ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ እና የኮሪደር ልማቶችን ጎብኝተዋል ። ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን ለመከላከልና ብልሹ አሰራሮችን ቀድሞ ከመቆጣጠር አንፃር በቴክኖሎጂ በታገዘ መልኩ የሚከወንና የስራ ባህልን የሚቀይር በመሆኑ በድሬዳዋ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል…

Read More

ኢትዮጵያ በቡድን 20 ጉባዔ ጥቅሟን የሚያስጠብቁ ውይይቶች አድርጋለች፦ አቶ አህመድ ሽዴ

በደቡብ አፍሪካ በተዘጋጀው የቡድን 20 (G-20) አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባዔ ላይ የኢትዮጵያ ጥቅም የሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ውይይት መደረጉን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ገለፁ። ከግሎባል ፈንድ ተጠቃሚ አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ፈንዱ በቀጣይ ዓመት የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ከ11 ቢሊዮን ዶላር በላይ ልገሳ እንዲደረግ ኢትዮጵያ ሰፊ ጥረት ማድረጓን ነው የገለፁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ…

Read More

ከካፍ ፕሬዝደንት ከዶክተር ፓትሪስ ሞትሲፒ በአፍሪካ እግር ኳስ እና ኢትዮጵያ በእድገቱ ስለሚኖራት ሚና ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። ለወጣቶች እድገት፣ የስፖርት መሠረተ ልማት ብሎም የአፍሪካን እግርኳስ በአለም መድረክ ለማላቅ ከካፍ ጋር ስለሚኖረን ትብብር ተወያይተናል።

Read More

ከኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዲክ ሾፍ ጋር በነበረን ውይይት በኢትዮጵያ እና ኔዘርላንድ መካከል ያለውን ጠንካራ ትስስር ለማጠናከር ውይይት አድርገን ነበር። ከኢትዮጵያ የውጭ ንግድ ቁልፍ መዳረሻዎች አንዷ የሆነችው ኔዘርላንድ ኢንቨስትመንት እና የኢኮኖሚ ትብብር ለማድረግ ጉልህ አቅም አላት። የአየር ንብረት ለውጥ ጥበቃ ሥራ ትብብርን አስመልክቶም እድሎቻችንን ለመመልከትና የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን በጉብኝቶች እና የልውውጥ መርሃ ግብሮች እንድንከውን በውይይቱ ሀሳብ አንስቻለሁ።

ጠቅላይ ሚንስተር አብይ አህመድ ( ዶ/ር)

Read More

ከብራዚል ፕሬዝደንት ሉዊዝ ኢናችዮ ሉላ ደ ሲልቫ ጋር ጥሩ ውይይት አድርገናል። ውይይታችን በኢኮኖሚ እና ዘላቂ የመሠረተ ልማት ጉዳዮች ላይ አተኩረን የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን የምናጠናክርባቸውን እድሎች አስመልክቶ የተካሄደ ነበር። ብራዚል በቅርቡ የተካሄደው የCOP30 አስተናጋጅ ሀገር እንደመሆኗ COP32ን በኢትዮጵያ ስናዘጋጅ ከብራዚል የምንወስደው ብዙ ጠቃሚ ልምዶች አሉ። የአለም የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራን የሚያራምድ በሚገባ የተሰናዳ መስተንግዶ እንዲኖረን ከልምዶች የተገኙ ሃሳቦችን መለዋወጡን አጠናክረን ለመቀጠል አቅደናል።

ጠቅላይ ሚንስተር አብይ አህመድ (ዶ/ር )

Read More