በ 8 የእግር ኳስ ቡድኖች መካከል ሲካሄድ የቆየው ‘ሳቢያን ካፕ’ ውድድር በታይዋን ቡድን አሸናፊነት ተጠናቀቀ
በድሬዳዋ የወረዳ ሁለት ወጣቶችና ስፖርት ማስተባበሪያ ከኢለፈንት ቢት ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጁትና ለ 8 ቀናት ሲካሄድ የቆየው የ “ሳቢያን ካፕ” ውድድር በዛሬው ዕለት ተጠናቋል። በዚህም በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የወረዳ 02 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አቤል ምስራቅ የሳቢያን ሲቲ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር 8 ቡድኖችን ባሳተፈ መልኩ ሲካሄድ መቆየቱን ገልፀው፤ ውድድሩ ወንድማማችነትን በማጠናከር ስፖርታዊ…


