የድሬደዋ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የ 9ኙ የከተማ ቀበሌ ስራ አስፈፃሚዎች የተሳተፉበት በአከባቢ ልማት እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረና ባለፉት አመታት የተከናወኑ የአከባቢ ልማት ስራዎች ዙሪያ ዉይይት ተካሄደ ፡፡ በዚህ የዉይይት ላይ የመክፈቺያ ንግግር ያደረጉት የኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ቢሮ ሀላፊ ኢንጂነር ጀማል በልማት ስራዎች ህብረተሰቡን አሳታፊ ማድረግ የልማት ስራዎቹን ህዝቡ በባለቤነት እየተከታተለ እንዲሰሩ ከማድረጉም በላይ ዘላቂ አገልግሎት እንዲሰጡም ያስችላል ብለዋል፡፡
ባለፉት አመታት የህብረተሰብ ተሳትፎና ልማት ኤጀንሲ የነበረዉ አደረጃጀት ፣ ያከናወናቸዉ ተግባራት በጎ ተግባራት እና የነበሩበት ዉስንነቶች እንዲሁም ከአደረጃጀቱ እና በቀበሌዎች ለአከባቢ ልማት ከሚሰበሰበዉ ሀብት ጋር ተያይዞ ያሉ ክፍተቶችን ያካተተ ጥናታዊ ፁሁፍ የድሬደዋ አስተዳደር የህብረተሰብ ተሳትፎና ልማት ኤጀንሲ ዳይሬክተር አቶ ጎንፋ ሞሲሳ ቀርቦ ዉይይት ተደርጎበታል፡፡
እያጋጠሙ ላሉ ተግዳሮቶች (ማነቆዎች) ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተሰጣቸውን ሃላፊነት በአግባቡ መወጣት የሚገባ መሆኑን እንዲሁም መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች ውጤት በሚያመጣ መልኩ መታረም እንዳለበትና የተጠያቂነት ስርዓትም መዘርጋት አለበት ተብሏል። በማጠቃለያ የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ ለኤጀንሲው የተሰጡ የስራ ሃላፊነትና መሰረታዊ ችግሮቹ ተፈትሸው ወደ ስራ እንዲገባ ይደረጋል ብለዋል ፡፡
ፈፎተቶ፡ ብልፅግና ፓርቲ ድሬደዋ የፌስቡክ ገጽ


