የኢፌድሪ ስራ እና ክህሎት ሚንስቴር ሚንስትር ዴኤታ በአቶ ሰለሞን ሶካ የተመራው ልዑክ ቡድን በአስተዳደሩ በቢዮአዋሌ ወረዳ ከተረጂነት ወደ ምርታማናት ለመሸጋገር የተከናወኑ ተግባራቶችን ጉብኝት እያካሄደ ነው ።

በድጋፋዊ ጉብኝቱም ከተረጂነት ለመውጣት በሚደረጉት ጥረት ውስጥ በ5 ጉዳዮችመግባባት፣በማዘጋጀት፣በማጥራት፣በማቀናጃት እና በማሻገር ላይ የተከናወኑ ተግባራት ትኩረት ተደርጎ ምልከታውን እንደሚያካሂድ የስራ እና ክህሎት ሚንስቴር ሚንስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ገልጸዋል።

የቢዬአዋሌ ወረዳ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ያሲን መሀመድ በወረዳው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር የተከናወኑ ተግባራቶችን እያቀረቡ ይገኛሉ።

በጉብኝቱም የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት ምክትል ና የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሻኪር አህመድ የዘርፉ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

ሰላም ለማ

ምስል፦ ሰላም አበበ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *