የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ግሽበቱን ለማረጋጋት ‘የኢትዮጵያን ይግዙ’ የንግድ ሳምንት ከፍተኛ አስተዋፆ እንዳለው ተገለፀ
በድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተዘጋጀው ሁለተኛው “የኢትዮጲያን ይግዙ” የንግድ ሳምንትን በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ተከፍቷል። የንግድ ሳምንቱ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ እንደሚካሄድ የገለፁት የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዲ ሙክታር ለአምስት ተከታታይ ቀናት ማለትም ከነሀሴ 12 እስከ ነሀሴ 16/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ አመላክተዋል።…


