“የኮሚዩኒኬሽን እና ሚዲያ ተቋማት የዲጂታል ዘመንን የሚመጥን ስራ ለመስራት ቅንጅታዊ አሰራርን ማሳደግ ይጠበቅባቸዋል፦” የድሬዳዋ የኮሚዩኒኬሽን ባለሞያዎች
የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ለህዝብ ግንኙነትና የኮሚዩኒኬሽን ባለሞያዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘመን ተግባቦት ላይ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ። በዚህም የስልጠናው ተሳታፊዎች ያለንበትን የዲጂታል ዘመን የሚመጥን ስራዎችን ሰርተን በምን መልኩ ለማህበረሰቡ ማቅረብ እንዳለብን ከስልጠናው እውቀቶችን ጨብጠናል በማለት የተናገሩ ሲሆን፤ የኮሚዩኒኬሽን እና ሚዲያ ተቋማት የዲጂታል ዘመንን የሚመጥን ስራ ለመስራት ቅንጅታዊ አሰራርን ማሳደግ እንደሚገባቸውም…


