ልዑክ ቡድኑ የድሬዳዋ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት ም/አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ከሪማ አሊ ፣ በም/ቤቱ ጸሀፊ የተከበሩ አቶ ማርቆስ ባዩህ እና በም/ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የምስራቅ አጎራባች ክልሎች የጋራ መድረክ የክልል መንግስታትን ግንኙነትን ማጠናከር ዓላማ ያደረገ ሲሆን መድረኩ፤የፌዴራል ከፍተኛ አመራሮች እና የአጎራባች ክልሎቹ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በነገው እለት በድሬዳዋ እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል።


