​የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጅሃር በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዛሬው ዕለት በግንባር ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።

ከንቲባው ድምፃቸውን የሰጡት በአስተዳደሩ ወረዳ 04 በሚገኘው ምርጫ ጣቢያ አንድ ነው። ​ከንቲባ ከድር ጁሃር ድምፅ በሰጡበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዜጎች በሕገ-መንግስቱ የተሰጣቸውን የመምረጥ መብት በአግባቡና በሃላፊነት ስሜት ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አሳስበዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በአገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ዝግጅት መደረጉን የገለጹት ከንቲባው፤ መላው ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥና የአገሪቱን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ…

Read More

የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ አደም ፋራህ ድሬዳዋ ገብተዋል::

ክቡር አቶ አደም ፋራህ ድሬዳዋ የገቡት በሶማሌ ክልል በሽንሌ ከተማ ድምፅ ለመስጠት ነው። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ አደም ፋራህ ድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ፣የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ኢብራሂም ይሱፍ እና የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

Read More