የአለም አቀፍ ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ በሀገራችን ከታየ ጊዜ ጀምሮ የመንግስትና የግል ትምህርት ተቋማት መዘጋታቸውን ተከትሎ ከ7 ወራት በኋላ ለማስጀመር በተቀመጠው መርሃ-ግብር በጥቅምት 9 በገጠር የሚገኙ ትምህርት ቤቶች እንደሚጀመሩ የተገለጸ ሲሆን በአስተዳደሩ ገጠር ቀበሌዎች የሚገኙ ት/ቤቶች እየተደረጉ ያሉትን ቅድመ ዝግጅቶችን በአስተዳደሩ ካቢኔ አባላት ጉብኝት ተደርገዋል፡፡
የጤና ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ለምለም በዛብህ በዋሂል ክላስተር የሚገኙ የበለዋና የለገ ኦዳ ት/ቤቶችን የመማሪያ ክፍሎች ጽዳትና ሊኖር የሚችለውን የተማሪዎች የክፍል ውስጥ አቀማመጥ እንዴት ሊሆን እንደሚችል ከት/ቤቶቹ አስተዳደር ጋር ተመካክረዋል፡፡
ክፍሎቹ ለትምህርት ዝግጁ ማድረጋቸውን የክላስተሩና የት/ቤቶቹ ኃላፊዎች የተናገሩ ሲሆን በተለይም ተማሪዎቹ በአንድ ክፍል እስከ 25 ተማሪ ርቀታቸውን ጠብቀዉ እንዲማሩበት ማዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል፡፡


