በጎነት ለወገን በሚል መሪ ቃል የድሬደዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሰራተኞችና አመራሮች መስከረም አስራ ስድስትን በተለያዩ የበጎ ስራ ተግባራት በመሰማራት እለቱን አስበው ውለዋል፡፡
በዚሁ እለትም ሰራተኞቹ የችግኝ መንከባከብ ለተቸገሩ ህፃናት የትምህርት መሳርያ ድጋፍ በማድረግና የህፃናት መንከባከቢያን በመጎብኘት እንዲሁም የደም ልገሳ መርሀግብር በማከናወን አሳልፈዋል፡፡ የድሬደዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ እስቂያስ ታፈሰ በወቅቱ እንደ ተናገሩት ተቋማት ከሚያከናውኑት የእለት ተእለት ተግባራት በተጓዳኝ በመሰል ማህበረሰብ ተኮር የበጎ አድራጎትና የማህበራዊ አገልግሎት ተግባራት በመሰማራት ለወገን አለኝታነታቸውን ማሳየት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ እኛም እንደተቋም…


