በድሬዳዋ አስተዳደር በ 2013 በጀት አመት ባለፍት 6 ወራት 157 ሚሊዮን ብር የሚገመት የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ ።በቀጣይም ኮንትሮባንድን ለመቆጣጠር ነዋሪው ህብረተሰብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባም ተገልፃል ።
በጉምሩክ ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅርንጫፍ በዋናነት ገቢን በመሰብሰብ ፣ ኮንትሮባንድን በመከላከልና የተለያዩ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ወደ ውጪ ሀገራት በመላክ ሀገራችን ኢትዮጲያ የውጪ ምንዛሬን እንድታገኝ ከማድረግ አኳያ ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል ። በዚህም መሰረት በ 2012 በጀት አመት ከ 6 . 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 8 . 4 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ ተችሏል ።…


