የድሬዳዋ ዩንቨርስቲ ሳምንታዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በዘጠኙም የከተማ ቀበሌዎች ለማካሄድ መዘጋጀቱ ተገለጸ::
የድሬዳዋ ዩንቨርሲት የዩንቨርሲቲውን ማህበረሰብ ተሳታፊ ያደረገ ወርሃዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በዛሬው እለት የ2ተኛ ዙር ፕሮግራሙንም በዩንቨርሲቲው በዋናው በር መግቢያ አካባቢ አካሂዷል፡፡ በአካል ብቃት እንቅስቃሴው የዩንቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣ መምህራንና ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ የአካል ብቃት እንቅስቃሴው በሀገር አቀፍ ደረጃ ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ የተሰጠውን ትኩረት መነሻ ማድረጉን በድሬዳዋ ዩንቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር…


