አለም አቀፍ የሴቶች ቀን በድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ በዉይይት ተከበረ።

    በአለም አቀፍ ደረጃ ለ110ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ45ኛ ጊዜ ዘንድሮ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ባለዉ የአለም ሴቶች ቀን በድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ
    “የሴቶች አመራር ሚና እና የኢትዮጲያ ብልፅግና ” በሚል መሪ ቃል በተካሄደዉ ውይይት ላይ የክብር እንግዳ የሆኑት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ሰሀለወርቅ ዘውዴ እንዳሉት የሴቶች ተሳትፎ እና ዕኩልነት ላይ አተኩረዉ ለሚሰሩ ጥናትና ምርምሮ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርጉ መሆኑን ገልፀዋል።
    የኢፌዴሪ የሴቶች፣ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ሚኒስተር ወ/ሮ ፊልሰን አብዱላሂ በበኩላቸዉ ማህበረሰቡ ሴቶች ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ተጠቃሚነት ለማሳደግ የወጣቱ ሚና ከፊተኛ ነዉ ብለዋል ፡፡
    የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም በበኩላቸዉ ዩኒቨርሲቲው የሴቶች ተሳትፎ እና ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ደረጃ ላይ የደረሱ ሴቶችን ከማበረታታት አንፃር ዘርፈ-ብዙ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸዉን አብራርተዋል፡፡